የቱርኩ ፕሬዚዳንት  ወደ  ኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉዞ ተራዝሟል ?

Date:

የቱርኩ ፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ቀጥሎም ወደ ኢትዮጵያ እንደሚያመሩ ተገልጾ ነበር።

በወጡት ሪፖርቶች ፕረዚደንቱ  ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ መሐመድ ቢንዛይድ የጤና ሁኔታ ጋር ተያይዞ ተራዝሟል። ሁለቱ የሀገር መሪዎች በስልክ ውይይት ማድረጋቸውም ነው የተገለጸው።

ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉዞስ ?

የቱርክ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ፕረዚዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉዞ እንደተጠበቀ ነው ሲል አስታውቋል።

ፕረዚዳንቱ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ግብዣ ወደ አዲስ አበባ እንደሚጓዙ የገለጹት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ ቡርሃኔትን ዱራን ውይይቶቹ በሁለትዮሽ ግንኙነቶች እንዲሁም በክልላዊ እድገቶች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ድርድር የተጠናቀቀባቸው እንደ ንግድ፣ የመከላከያ የተለያዩ  መሠረተ ልማቶች ላይ ስምምነቶች እና ሰነዶች እንደሚፈረሙ ይጠበቃል ሲሉም አክለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...