የቴሌብር ጥምረት ከሱዳንና ጅቡቲ ጋር!

Date:

ኢትዮ ቴሌኮም ከሱዳንና ጅቡቲ ጋር ክልላዊ የክፍያ ትስስር ለመፍጠር እያካሄድው ያለው ድርድር፣ ኢትዮጵያ የቀጣናው ቁልፍ ተዋናይና በምሥራቅ አፍሪካ እንዲሁም በአህጉሪቱ የኢኮኖሚ ውህደት ጉልህ ሚና መጫወት እንደምትችል የሚያሳይ መሆኑን የስፑትኒክ ትንተና ይጠቁማል፡፡

የክፍያ ስርዓቱ ለሀገራቱ ምን ይፈይዳል? ቁልፍ ዝርዝር ጉዳዮች፦

*ቀልጣፋ ግብይት፦ ትስስሩ በሀገራቱ መካከል የሚደረገውን ግብይት እስከ እጅ ስልክዎ ያሳጥራል፣

*ተመጣጣኝ የአገልግሎት ክፍያ፦ በዓለም አቀፍ ገንዘብ አስተላላፊዎች በኩል የሚፈጸሙ ግብይቶችን ያርቃል፣

*በራስ ገንዘብ መገበያየት፦ ቴሌብርን ከፓን አፍሪካ የግብይትና ክፍያ ስርዓት ጋር በማዋሃድ የሚቀርበው አገልግሎቱ፤ በሀገራቱ መካከል የሚደረገውን ግብይት ከዶላር ጥገኝነት ነፃ ሊያወጣ እንደሚችል ትንተናው ያመለክታል፡፡

ለምን ሱዳንና ጁቡቲ?

የሱዳን የዲጂታል የክፍያ ተቋማት በዓለም አቀፍ ደረጃ አገልግሎት የሚሰጡ በመሆኑ ከቴሌብር ጋር የሚኖረውን ጥምረት ያቀለዋል። ከኢትዮጵያ የገቢ ወጪ መስመር ጅቡቲ ጋር ኢኮኖሚያዊ ትስስርም ይበልጥ ይጠነክራል።

ኢትዮ ቲሌኮም በበጀት ዓመቱ በቴሌብር 2.38 ትሪሊየን ብር የተዘዋወረ ሲሆን፤ አገልግሎቱ ከተጀመረ ጀምሮ በኢኮኖሚው ውስጥ 4.93 ትሪሊየን ብር ማዘዋወር እንደቻለ ስፑትኒክ አስታውሷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...