የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

Date:

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት ገንዘብ ላይ የአሜሪካው የገቢዎች ባለስልጣን (IRS) የታክስ ድርሻ መጠየቁ አከራካሪ ሆኗል።

ውድድሩን በጋራ ያዘጋጁት ሜክሲኮና ካናዳ ለተሳታፊ ቡድኖች ሙሉ የታክስ ነፃ መብት የሰጡ ቢሆንም፣ አሜሪካ ግን “በግዛቴ ውስጥ የተገኘ ማንኛውም ገቢ ታክስ ይከፈልበታል” በሚለው ህጓ በመፅናቷ ቡድኖቹን ለከፍተኛ ክፍያ ዳርጋቸዋለች።

በመደበኛው ህግ መሰረት ከአሜሪካ በሚገኝ ገቢ ላይ 30% የታክስ ተቀናሽ የሚደረግ በመሆኑ፣ ስፔን ከ50 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት ገንዘብ ውስጥ እስከ $15 ሚሊዮን ዶላር ልታጣ ትችላለች።

ይሁን እንጂ ትክክለኛው የታክስ መጠን የሚወሰነው ስፔን በሶስቱ አዘጋጅ ሀገራት በነበራት የጨዋታዎች ብዛት ድርሻ ነው። ይህንን ውዝግብ ለመፍታት የአሜሪካ እና የካናዳ የታክስ ተቋማት የሽልማት ገንዘቡ ታክስ እያንዳንዱ ቡድን በየሀገራቱ ባደረገው የጨዋታዎች ብዛት ተሰልቶ እንዲከፋፈል ተስማምተዋል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...