የቻይና የመርከብ ግንባታ ኮርፖሬሽን በጂያንግዙ ግዛት የጫነውን ጭነት በራሱ የሚያራግፍ የአለማችንን ፈጣኑን መርከብ በይፋ ስራ ማስጀመሩን ሲጂቲኤን ዘግቧል።
ይህ ግዙፍ መርከብ 215 ሜትር ርዝመትና 42 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን፣ ከ41 ሺህ ቶን በላይ ክብደትና 29 ሺህ ኪዩቢክ ሜትር ጭነት የመያዝ ከፍተኛ አቅም እንዳለው ተገልጿል።
ይህ ዘመናዊ መርከብ በሰአት እስከ 12 ሺህ ቶን ጭነት የማራገፍ አስደናቂ ብቃት ያለው በመሆኑ በአለም የመጀመሪያው ፈጣን የመርከብ ስያሜን ተጎናጽፏል።
እንደነዚህ ያሉ የቴክኖሎጂ ምጥቀቶች በዓለም አቀፍ የባህር ላይ ጭነት እና ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ላይ ከፍተኛ እና አዎንታዊ ለውጥ እንደሚያመጡ ተመላክቷል።
