የአበበች ጎበናን ህይወት የሚተርክ ፊልም ተመረቀ

Date:

የአበበች አደራ” በሚል ስያሜ እንዲሁም “ፍቅር፣ ርህራሄ፤ ወደር የማይገኝለት ሰብዓዊነት!”በተሰኘ መሪ ቃል ህይወት የሚተርክ ፊልም ምርቃት እና ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር  በትናትናዉ  እለት ተካሄዷል።

መርሐ ግብሩ ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና የሚታወሱባቸውንና ትውልድ ሊያውቀውና ሊማርበት የሚገባ የህይወታቸው እሴቶችና መርሆዎችን ለማስገንዘብ እንዲሁም ለትውልድና ለኢትዮጵያ መንግስት አደራ ሰጥተው የሄዱትን ድርጅት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው፡፡

የክብር ዶክተር አበበች ጎበና የአበበች ጎበና ቻሪቲ መስራችና ባለራዕይ ሲሆኑ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን በማሳደግና በአያሌ የሰብዓዊነት ተግባራቸው በመላው ዓለም እውቅናን ያገኙ ሰው ናቸው፡፡

በ1972 ዓ.ም ወላጆቻቸው በረሀብ የሞቱባቸው ሁለት ህፃናትን በማንሳት የተጀመረው ጉዞ ከአርባ ሰባት ዓመታት በኋላ እንኳ ብዙዎች የሚጓዙበት የርህራሄና የሰብዓዊነት ጎዳና ሆኖ ቀጥሏል፡፡

ከአመታት በፊት በኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈው እኒህ ታላቅ እናት በስራ ወዳድነታቸው፤ በደግነታቸውና በሰብዓዊ ተግባራቸው በትውልዶች ይታወሳሉ፡፡ ስራቸውም በአያሌ ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው ህያውነት ውስጥ ተጠብቆ ይኖራል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...