“ከጦር ይልቅ ዲፕሎማሲ ሰርጡን ይከፍታል “ህንድ

Date:


ህንድ “የሆርሙዝ ሰርጥን ዳግም ለመክፈት ዲፕሎማሲ ቁልፍ ጉዳይ ነው “አለች።

ኒው ደልሂ ከወታደራዊ አካሄድ ይልቅ ዲፕሎማሲን መከተል ከኢራን ጋር ያለውን ልዩነት እንደሚፈታ አሳስባለች።

በሆርሙዝ ሰርጥ መርከቦችን እንደወትሮው ለማንቀሳቀስ ከቴህራን ጋር መወያየት ወሳኝነት ያለው ጉዳይ ነው ተብሏል።

የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኒው ደልሂና በቴህራን መካከል በተደረገ ድርድር ሁለት የህንድ ባንዲራን የያዙ  መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ እንዲያልፉ ተፈቅዶላቸዋል የሚለውን በማሳያነት አንስተዋል።

በሌላ በኩል የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በዚሁ ሰርጥ ዙሪያ ተወያይተዋል።

ዳውኒንግ ስትሪት መሪዎቹ የሆርሙዝ መከፈትን አስፈላጊነት ትኩረት ሰጥተው መምከራቸንም አሳውቋል።

ስታርመር ከካናዳው አቻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ካርኔይ ጋርም በቀጠናው ቀውስ እና በሆርሙዝ ሰርጥ ጉዳይ   መወያየታቸው ተሰምቷል።

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰይድ አባስ አራግቺም “ለድርድር ዝግጁ አይደለንም
፣ለረዥም ጦርነት ቴህራን ተዘጋጅታለች” ማለታቸው የሁኔታውን መወሳሰብ ጠቋሚ ያደርገዋል።

ዘገባው የአልጀዚራና ዋሽንግተን ፖስት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...