በሀብት መጠኑ የኬንያ ቁንጮ የሆነው ኬሲቢ ግሩፕ፣ የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለመቀላቀል የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናቆ የሚገዛውን የሀገር ውስጥ ባንክ መለየቱን በይፋ አስታውቋል።
ባንኩ በ2025 ያስመዘገበው የ544 ሚሊዮን ዶላር ሪከርድ ትርፍ ለዚህ ትልቅ ኢንቨስትመንት ጉልበት ሆኖታል።
ኬሲቢ አዲስ ባንክ ከመክፈት ይልቅ ነባር ባንክን በመግዛትና የአብላጫ ባለቤትነት ድርሻን በመያዝ፣ የኢትዮጵያን 120 ሚሊዮን ሕዝብ ያቀፈ ግዙፍ ገበያ በአጭር ጊዜ ለመቆጣጠር አቅዷል።
ባንኩ የገዛውን የኢትዮጵያ ባንክ ማንነት በዚህ ዓመት መጨረሻ ይፋ የሚያደርግ ሲሆን፣ አጠቃላይ ሂደቱን እስከ 2026 ማብቂያ አጠናቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይጠበቃል።
ኬሲቢ እንደ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሁሉ ትኩረቱን በዲጂታልና በሞባይል ባንክ አገልግሎት ላይ በማድረግ ሰፊ የቅርንጫፍ ግንባታ ወጪዎችን ለማስቀረት ወጥኗል።
ይህ የኬሲቢ ግስጋሴ እንደ ስታንዳርድ ባንክ እና አብሳ ግሩፕ ያሉ ሌሎች የአፍሪካ የፋይናንስ ግዙፎችም ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት አይናቸውን በጣሉበት ወቅት የተሰማ ትልቅ ዜና ሆኗል።
