የአቡ ዳቢ ፖሊስ ከ100 በላይ የተለያዩ አገራት ዜጎችን በቁጥጥር ስር አዋለ

Date:

በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ የአቡ ዳቢ ፖሊስ የተለያዩ አገራት ዜግነት ያላቸው ከ100 በላይ ሰዎች በአገሪቱ ላይ ከሚፈጸመው ጥቃት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ቦታዎችን “በመቅረጽ እና አሳሳች መረጃን” በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በማጋራት መያዙን አሳወቀ።

ፖሊስ በኤክስ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ የተለያዩ 109 ሰዎች በሕዝቡ መካከል የተሳሳተ አመለካከትን የሚፈጥሩ እና ያልተረጋገጡ ወሬዎችን በማሠራጨት በቁጥጥር ስር አውሏል።

ፖሊስ ጨምሮም ማኅበራዊ ሚዲያን ተገቢ ላልሆነ ዓላማ የሚጠቀሙ ሰዎችን በመከታተል የአገሪቱ የደኅንነት ባለሥልጣን አስፈላጊው ሕጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቋል።

የአገሪቱ ዜጎች ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት እና ከሚታመኑ ምንጮች ብቻ መረጃ እንዲያገኙ በማሳሰብ የሕዝብ ጥቅምን እና አሠራሮችን በማክበር ከአንዳንድ ቦታዎች “ፎቶ ከማንሳት እና ቪዲዮ ከመቅረጽ እንዲሁም ከማጋራት እንዲቆጠቡ” አሳስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...