የኢስፋሃን አስተዳዳሪ መህዲ ጃማልላይጃድ አገራቸው ከእስራኤል እና ከአሜሪካ ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት “21 ታሪካዊ ቅርሶች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል” ሲሉ ተናገሩ።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን ጃማልላይጃድ ጠቅሰው ጉዳቱ “በቅርሶች ላይ 500 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ውድመት” ማድረሱን ዘግበዋል።
አስተዳዳሪው የኢስፋሃንን ታሪካዊ ቅርሶች መጠበቅ “ብሔራዊ ኃላፊነት ነው” ማለታቸው የተዘገበ ሲሆን፣ የደረሰውን ጉዳት በሚመለከት “ካሳ እና ለመጠገን የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች ሕጋዊ በሆነ መልኩ በሚመለከታቸው አካላት በኩል” እንደሚጠይቁ ተናግረዋል።
