“የአፍሪካ ትምህርት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ መውጣት አለበት”

Date:

በቅኝ ግዛት ተጽዕኖ ሥር ያለው የአፍሪካ የትምህርት ሥርዓት ከሀገር በቀል ዕውቀት ይልቅ ለምዕራባውያን ሞዴሎች ቅድሚያ ስለሚሰጥ ማኅበረሰቦች ችግሮቻቸውን በራሳቸው መንገድ እንዳይፈቱ አድርጓቸዋል ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎት እና አካታች ትምህርት ክፍል ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አለማየሁ ተክለማርያም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

📜 አክለውም ቋንቋ ለመረዳት እና ችግር ለመፍታት ቁልፍ በመሆኑ ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር አለባቸው ብለዋል። እውነተኛ እውቀት የሚገኘው ከሀገር በቀል አስተሳሰብ እና ማኅበረሰብ ላይ በተመሠረተ ምርምር እንደሆነ የገለፁት ፕሮፌሰሩ፤ ይህም ወደ አካባቢያዊ ፈጠራ እና ቴክኖሎጂ ሊያመራ እንደሚችል አስረድተዋል።

“ኢትዮጵያ በወታደራዊ ኃይል በጭራሽ ቅኝ አልተገዛችም፤ ነገር ግን ባህላችን ቅኝ ተገዝቷል። ስለዚህ አስተሳሰባችንን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ማውጣት አለብን” ሲሉ ፕሮፌሰር ተክለማርያም ተናግረዋል።

📖 ፕሮፌሰሩ በቲክቶክ፣ ዩቲዩብ እና የውጭ ሚዲያዎች የተተኩት የአፍሪካ ባሕሎች እና የቃል ወጎች መነቃቃት እንደሚያስፈልጋቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...