የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ፈቃድ ሰጠ

Date:

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ለማሳደግና የሎጅስቲክስ ዘርፉን ለማጠናከር በማለም ለሶስት ተጨማሪ ኩባንያዎች የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የስራ ፈቃድ ሰጠ።

ፈቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች ኢትዮ ሬል ሎጅስቲክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ትራንስፖርት አክስዮን ማህበር እና ገልፍ ኢንጎት ኤፍ ዜድ ሲ ኢንደስትሪስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ናቸው።

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት (ዶ/ር) ፣ ተጨማሪ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ መግባታቸው በገበያው ውስጥ ፉክክርን በማነቃቃትና በትብብር በመስራት የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያደርጋል።

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ በበኩላቸው፣ የመልቲ ሞዳል አገልግሎት ወጪን በመቀነስ እና የገቢ ዕቃዎች ደህንነትን በመጠበቅ በፍጥነት ወደ ተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

በአጠቃላይ፣ የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ዘርፉን የተቀላቀሉ ኦፕሬተሮች ቁጥር ወደ ሰባት አድጓል። በቅርቡ ዘርፉን የተቀላቀሉት ኦፕሬተሮች ፓናፍሪክ ግሎባል፣ ጥቁር አባይ ትራንስፖርት እና ኮስሞስ መልቲ ሞዳል ኦፕሬሽን የተሰኙ ኩባንያዎች መሆናቸዉ ይታወቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...