የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ፈቃድ ሰጠ

Date:

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ለማሳደግና የሎጅስቲክስ ዘርፉን ለማጠናከር በማለም ለሶስት ተጨማሪ ኩባንያዎች የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የስራ ፈቃድ ሰጠ።

ፈቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች ኢትዮ ሬል ሎጅስቲክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ትራንስፖርት አክስዮን ማህበር እና ገልፍ ኢንጎት ኤፍ ዜድ ሲ ኢንደስትሪስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ናቸው።

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት (ዶ/ር) ፣ ተጨማሪ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ መግባታቸው በገበያው ውስጥ ፉክክርን በማነቃቃትና በትብብር በመስራት የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያደርጋል።

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ በበኩላቸው፣ የመልቲ ሞዳል አገልግሎት ወጪን በመቀነስ እና የገቢ ዕቃዎች ደህንነትን በመጠበቅ በፍጥነት ወደ ተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

በአጠቃላይ፣ የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ዘርፉን የተቀላቀሉ ኦፕሬተሮች ቁጥር ወደ ሰባት አድጓል። በቅርቡ ዘርፉን የተቀላቀሉት ኦፕሬተሮች ፓናፍሪክ ግሎባል፣ ጥቁር አባይ ትራንስፖርት እና ኮስሞስ መልቲ ሞዳል ኦፕሬሽን የተሰኙ ኩባንያዎች መሆናቸዉ ይታወቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...