የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ሠራተኞች፤ አመራርና ተገበያዮች 129ኛውን የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አከበሩ

Date:

129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል የምርት ገበያው አመራሮች፣ ሠራተኞችና ተገበያዮች በተገኙበት የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በምርት ገበያው ዋና መሥሪያ ቤት ተከበሯል፡፡

በክብረ በዓሉ ላይ አቶ መርጊያ ባይሣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መልዕክት ያስተላለፉ ሲኾን አባቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነት ነፃነትና ክብር ያላት ሀገር በመረከባችን ዕድለኞች ነን፣ ለዚህ ክብር ያበቁን ጀግኖች አባቶቻችን ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡

አድዋ የጥቁር ህዝቦች የነጻነትና የጀግንነት መገለጫ ነው፡፡  የዚህ ዘመን ትውልድ የአባቶቻችንን አደራ በመረከብና ዘመኑ የሚጠይቀውን ጀግንነት በመፈፀም ሀገራችን ወደ ብልፅግና ለመሻገር የሚደርገውን ጥረት በባለቤትነት የማሳካት አደራ አለበት ብለዋል፡፡

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለው የምርት ገበያው አመራሮች፣ ሠራተኞችና ተገበያዮች በተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ በታማኝነትና በትጋት በማገልገል የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ተምሳሌት የሆነቸውን ሀገራችን ኢትዮጵያን  የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት ለማሳካት ከምን ጊዜውም በላይ ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለክብረ በዓሉን  የተዘጋጀውን የመወያያ ሰነድ አቶ ዳዊት ሙራ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቅርበገው ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...