የኢትዮጵያ ሪድስ አምስተኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው

Date:

ለዓመታት የልጆች የንባብ ልምድ ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ የሚገኘው ኢትዮጵያ ሪድስ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው አምስተኛ ጉባኤው ከትላንት መጋቢት 24 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።

በዝግጅቱ ላይ ከተለያየ ዘርፍ የተወጣጡ ባለሙያዎች ስለ ልጆች ንባብ እና ተያያዥ ሀሳቦች ላይ መነሻ ጥናታዊ ፅሁፎች እያቀረቡ ሲሆን በፅሁፎቹም መነሻነት የሃሳብ ልውውጥ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ጉባኤ ላይ የልጆች ንባብ ባህልን ለማሳደግ አስተዋፅኦ ያደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና የመስጠት መርሃግብር ይካሄዳል ተብሏል።

ኢትዮጵያ ሪድስ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ በሀገሪቱ በሁሉም ክልሎች ከ70 በላይ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ቤተመጽሐፍትን በማቋቋም ከመንግስት እና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር አብሮ እየሰራም እንደሚገኝ አስታውቋል።

የ22 ዓመታት እድሜ ያስቆጠረው ኢትዮጵያ ሪድስ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች እና ልጆችን ባለፉት ዓመታት በንባብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረጉን ገልጿል።

📸 ተክሌ ማርኮን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...