የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በይፋ ስሙን ቀየረ

Date:

ተጠሪነቱ ለትምህርት ሚኒስቴር የሆነው የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፤ የትኩረት አቅጫውን በሚጠቁም መልኩ ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ “የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ“ በሚል ስያሜ የሚጠራ መሆኑን ገልጿል፡፡

የስያሜ ለውጡ ተቋሙ በፐብሊክ ሰርቪስ ትምህርት፣ ምርምር እና አመራር የልህቀት ማዕከል ለመሆን የያዘውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

በዚህም የዩኒቨርሲቲው ይፋዊ ድረ-ገፅ እና የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በአዲሱ ስያሜ የሚቀየሩ ሲሆን፤ የተቋሙ ሰራተኞች እንዲሁም የቀድሞ እና የአሁን ተማሪዎች አዲሱን ስያሜ እንዲጠቀሙ ተጠይቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ እና ከፐብሊክ ሴክተር ተቋማት የተመለመሉ ተማሪዎችን በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች መቀበሉ ይታወቃል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...