የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን አገልግሎት ላይ ሊያውል ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አርቸር አቪዬሽን በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ለማዋል የሚያስችል የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ።
ስምምነቱ ዘመኑ የደረሰበትን የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ከማስቻሉም በላይ ለአየር ንብረት መጠበቅ የራሱ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ከአየር መንገዱ ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
