የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለቪ.አይ.ፒ እና ልዩ ቻርተር በረራ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ቦይንግ 737-800 ቢዝነስ አውሮፕላን መረከቡን ሲገልጽ ደስታ ይሰማዋል።
ይህ የቢዝነስ አውሮፕላን በተለይም በአፍሪካ የንግድና ኢንቨትመንት ስራዎቻቸውን ለማሳለጥ በርካታ ጉዞዎችን ለሚያደርጉ በከፍተኛ ንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦች፣ ድርጅቶች እና ደረጃውን የጠበቀ ልዩ ልዩ የቻርተር በረራ አገልግሎት ለሚሹ ተጓዦች በሙሉ አየር መንገዱ ልዩ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችለዋል።
በአቀባበል ስነስርዐቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የቦይንግ ኩባንያ ተወካዮች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተወካዮች ተገኝተዋል። ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ።
