የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ከተሞች የሚያደርጋቸው በረራዎች መሰረዛቸው ተሰማ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች አየር ማረፊያዎች የሚያደርጋቸው በረራዎች መሰረዛቸው ተነገረ።

ቢቢሲ ትግርኛ ሐሙስ ጥር 21/2018 ዓ.ም. ወደ ትግራይ ክልል የሚደረጉ በረራዎች መቋረጣቸውን ከተጓዦች እና ከክልሉ አንድ ኃላፊ ማረጋገጥ ችሏል።

ለዛሬ ተይዘው በነበሩ በረራዎች ወደ አዲስ አበባ ለመጓዝ ትኬት ቆርጠው የነበሩ መንገደኞች የሐሙስ ጥር 21/2018 ዓ.ም. መሰረዛቸውን የሚያስታውቅ አጭር የጽሁፍ መልዕክት እንደደረሳቸው ተናግረዋል።

በመልዕክቱ ላይ “ከዕቅድ ውጪ በመሆነ ምክንያት” በረራው መሰረዙን እና መንገደኞች የኢትዮጵያ አየር መንገድን ወይም የጉዞ ወኪላቸውን እንዲያገኙ መክሯል።

ነገር ግን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራዎቹን መቋረጥን በተለመከተ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ምክንያትም ሆነ መግለጫ የለም።

ስለ በረራዎች መሰረዝ የተጠየቁት የክልሉ ትራንስፖርት ኃላፊ አቶ ታደለ መንግሥቱ በረራዎች መቋረጣቸውን አረጋግጠው፤ ነገር ግን ዝርዝር መረጃ እንደሌላቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ተጠቃሚዎች የደረሳቸው የፅሑፍ መልዕክት

ቢቢሲ ከአየር መንገዱ ይፋዊ ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አስካሁን ምላሽ አላገኘም፤ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የአየር መንገዱ ኃላፊ ግን ወደ ትግራይ የሚደረጉ በረራዎች መቋረጣቸውን አረጋግጠዋል።

እኚሁ የአየር መንገዱ ባልደረባ እንደገለጹት “በረራዎች ለዛሬ [ሐሙስ] ብቻ ነው የተሰረዙት፤ ነገር ግን የቀጣይ ቀናት በረራዎች በሚኖረው ሁኔታ የሚወሰን ይሆናል” በማለት ለውሳኔው ምክንያቱ ምን እንደሆነ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...