የኢትዮጵያ አየር መንገድ 21ኛውን ኤርባስ A350-900 አውሮፕላን መረከቡን ገለፀ

Date:

አየር መንገዱ ዛሬ የተቀበለው ኤርባስ A350-900 አውሮፕላን እጅግ ዘመናዊ እና እስከ 340 ሰዎችን መመጫን አቅም ያለው ነው።

አዲሱ አውሮፕላን አየር መንገዱ ለደንበኞች  እየሰጠ ያለውን አስተማማኝና ምቹ  አገልግሎት ይበልጥ የሚያጠናክር እና በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ያለውን የመሪነት ሚና የሚያስቀጥል ነው ተብሏል።

አፍሪካን ከዓለም በማገናኘት አንጋፋነቱን ማስቀጠል የቻለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደፊትም ሌሎች ኤርባስ A350-900 እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን ለመቀበል በሂደት ላይ ይገኛል።

የስታር አሊያንስ አባል የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመንገደኞች፣  በጭነት፣  በመስተንዶ፣ ለደንበኞች አስተማማኝ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ሽልማቶችን ማሸነፉ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ተወዳዳሪነቱን እና መሪነቱን ለማስቀጠል በ10 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በቢሾፍቱ የግዙፍ ዓለመ አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...