የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ከአውሮፓ ኅብረት ጋር

Date:

የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ(ተባባሪ ፕሮፌሰር) ከአውሮፓ ኅብረት የግሉ ዘርፍ፣ የንግድ፣ ኢኮኖሚ እና አካባቢያዊ ትስስር ጉዳዮች ፕሮግራም ኦፊሰር አድሪያን ካኖ ጉሬሮ ጋር ተወያዩ፡፡


ሁለቱ አካላት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን ምክር ቤቱ በሴቶች የቢዝነስ አመራር፣ በቻምበር የዲጂታይዜሽን ስርዓት፣ በቢዝነስና ሰላም፣ በአቅም ግንባታ፣ በአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች አቅም መጎልበት እንዲሁም በወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ዙሪያ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ እየሰራ መሆኑን ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ አብራርተዋል፡፡

በሌላ በኩል የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ ኢኮኖሚያዊ ስራዎች አስፈላጊውን እገዛ እያደረገ ሲሆን ከምክር ቤቱ ጋርም የሚሰሯቸውን ስራዎች አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ሚስተር አድሪያን ተናግረዋል፡፡


ከዚህ በፊትም የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ከአውሮፓ ኅብረት ጋር በመተባበር በተለያዩ ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸው ተጠቁሟል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...