የኢትዮጵያ ግብርና ሜካናይዜሽን ምርታማነትን በከፈተኛ ሁኔታ እያሳደገ እንደሆነ ተገለፀ

Date:

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ ባለፈው የመኸር ወቅት ከታረሰው 20.5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ 25 በመቶው በትራክተር መታረሱን ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ የግብርና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት መንግሥት የፖሊሲ እርምጃዎችን እንደወሰደም ጠቅሰዋል። ለአብነትም የእርሻ ማሽነሪዎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ለአርሶ አደሮች ተደራሽ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ግብዓትን በራስ አቅም በመሸፈን ለግብርናው ዘርፍ አዲስ የታሪክ እጥፋት ያመጣል ብለዋል ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በፓርላማ ቀርበው ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፤ መንግሥት ከውጭ የሚያስገባውን የአፈር ማዳበሪያ ለመተካት የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ማቀዱን ገልፀዋል።

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የክሪፕቶ ሥራ ፈጣሪው የ15 ዓመት እስር ተፈረደበት

የቀድሞው የክሪፕቶከረንሲ ሥራ ፈጣሪ ተሰውሯል ከተባለ 40 ቢሊየን ዶላር...

5ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ...

የንግድ ሚኒስቴር 13 ምርቶችን በመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ (PVoC) እንዲያገኙ ወሰነ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ በሀገር...

ገዳ ባንክ ከ444 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች የተከፈለ ካፒታላቸውን በ2018 ዓ.ም...