የኢትዮጵያ ግብርና ሜካናይዜሽን ምርታማነትን በከፈተኛ ሁኔታ እያሳደገ እንደሆነ ተገለፀ

Date:

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ ባለፈው የመኸር ወቅት ከታረሰው 20.5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ 25 በመቶው በትራክተር መታረሱን ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ የግብርና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት መንግሥት የፖሊሲ እርምጃዎችን እንደወሰደም ጠቅሰዋል። ለአብነትም የእርሻ ማሽነሪዎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ለአርሶ አደሮች ተደራሽ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ግብዓትን በራስ አቅም በመሸፈን ለግብርናው ዘርፍ አዲስ የታሪክ እጥፋት ያመጣል ብለዋል ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በፓርላማ ቀርበው ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፤ መንግሥት ከውጭ የሚያስገባውን የአፈር ማዳበሪያ ለመተካት የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ማቀዱን ገልፀዋል።

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...