የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

Date:

የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የቦርድ አባላት የእስራኤል ወታደራዊ ጥቃት በኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚያስከትለውን አደጋ ለመወያየት ዛሬ በኤጀንሲው ዋና መሥሪያ ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ያደርጋሉ።

ስብሰባው የተጠራው በኢራን ሲሆን የሩሲያ፣ቻይና እና ቬንዙዌላን ድጋፍ አግኝቷል።

ኢራን መጀመሪያ ላይ በሳምንቱ መጨረሻ የእስራኤልን ጥቃት የሚያወግዝ የውሳኔ ሃሳብ ማቅረብ ፈልጋ ነበር።

ይሁንና ቢቢሲ ያነጋገራቸው የዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደገለፁት የውሳኔ ሃሳቡ የብዙሃኑን ድጋፍ ያስገኛል ተብሎ አይታሰብም።

በዚህም ምክንያት ኢራን አሁንም የእስራኤልን ድርጊት ማውገዝን ያካተተ አጠቃላይ መግለጫ ለማቅረብ ተዘጋጅታለች።

ይህ አስቸኳይ ስብሰባ የተጠራው በኢራን እና በእስራኤል መካከል እየተካሄደ ያለው የሚሳዔል ልውውጥ መካከል እስራኤል በናታንዝ እና ፎርዶው የሚገኙ የኢራን የኒውክሌር ቦታዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መሰንዘሯን ተከትሎ ነው።

የኒውክሌርን ስጋት ለመፍታት ወታደራዊ እርምጃ በኤጀንሲው አባል አገራት ስምምነት መሠረት ተቀባይነት ያለው መንገድ ሆኖ አያውቅም።

ኢራን ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እና የኤጀንሲው የቦርድ አባላት ጥቃቱን ማውገዝ እንዳለባቸው አጥብቃ ትናገራለች።

ሆኖም አሁን ካለው የፖለቲካ ሁኔታ አንፃር እንዲህ ዓይነቱ ውግዘት የሚጠበቅ አይደለም።

በተጨማሪም ይህ ስብሰባ በሁለቱ ኃያላን አገራት መካከል በአፋጣኝ የተኩስ ማቆም እንዲደረግ መንገድን ስለ መክፈት አለመክፈቱ ግልፅ አይደለም።

ሁለቱ አገራት አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጠንካራ የአጸፋ ጥቃት መስጠታቸውን ቀጥለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...