የግብይትና የታክስ ህጎችን ባላከበሩ 11 ሺህ 283 ነጋዴዎች ርምጃ ተወስዷል

Date:

3ኛው የአዲስ አበባ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫን አቅርበዋል።

ከንቲባዋ ገቢና ወጪን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ በ2017 በጀት ዓመት ከ233 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን አስታውቀዋል።

የተሰበሰበው ገቢም ከ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ83.3 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።

በገቢ አሰባሰብ ሂደቱ የሌብነትና ብልሹ አሰራር በፈጸመው 247 ሰራተኞች ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም ተናግረዋል፡፡

ባለፉት 11 ወራት የግብይትና የታክስ ህጎችን በላከበሩ እና ደረሰኝ ባልሰጡ 11 ሺህ 283 ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም አመላክተዋል።

በጋዜጣ_ፕላስ |

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...