የፈረንሳዩ ካናል ፕላስ መልቲ ቾይስን በ3 ቢ. ዶላር ጠቅልሎ ገዛው

Date:

ታዋቂው የፈረንሳይ የሚዲያ ግዙፍ ኩባንያ ካናል ፕላስ፣ የዲኤስቲቪ እና የጎቲቪ የላይኛው ኩባንያ የሆነውን የደቡብ አፍሪካውን መልቲቾይስን በ3 ቢሊዮን ዶላር ለመግዛት ያደረገውን ስምምነት በይፋ አጠናቋል።

ይህ ግዙፍ ግዢ መጠናቀቁን ተከትሎ፣ መልቲቾይስ ሙሉ በሙሉ የካናል ፕላስ እህት ኩባንያ  ሆኗል። ኩባንያው ከዚህ ውሳኔ በኋላ በመላው አፍሪካ በዲጂታል የፊልም ማሰራጫዎች፣  በቴክኖሎጂ፣ በአገር በቀል የአፍሪካ ይዘቶችና በስፖርት ስርጭቶች ላይ በከፍተኛ ደረጃ መዋዕለ ንዋይ እንደሚያፈስ አስታውቋል።

ይህ ታሪካዊ ግዢ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የሚዲያና የመዝናኛ ኩባንያዎች መካከል አንዱን የሚፈጥር ሲሆን፣ ካናል ፕላስ በፍጥነት እያደገ ባለው የአፍሪካ የሚዲያና የዲጂታል ስርጭት ገበያ ውስጥ ያለውን የበላይነትና ተሰሚነት ይበልጥ ያጠናክረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

በአህጉሪቱ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የዲኤስቲቪ ተጠቃሚዎችም በዚህ አዲስ ውህደት ሳቢያ ሰፊና ጥራት ያላቸው ይዘቶችን ለማግኘት አዲስ ዕድል እንደሚከፍትላቸው ተነግሯል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...