‘’የፌደራል መንግስት ሊያማክረን ይገባል’’ የትግራይ ጊዜያዊ አማካሪ

Date:

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትን ህዝቡ እንዲመርጥ የሰጡት እድል ለዲሞክራሲ የቀረበ ቢሆንም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤቱን ያገለለ ነው ሲሉ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ለሃገሬ ቴሌቪዥን ቅሬታቸውን አቀረቡ፡፡

የትግራይ ነጻነት ፓርቲ የጽህፈት ቤት ሃላፊ ጣዕመ ሃጎስ፣ የፌደራል መንግስት የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትን ህዝቡ በኢሜይል እንዲመርጥ መጠየቃቸው ሌሎች ከክልሉ ውጪ ያሉ አካላትም እንዲመርጡ የሚያደርግ በመሆኑ ስህተት እንደሆነ አንስተዋል፡፡

አካሄዱ የተለያዩ የትግራይ ጉዳይ የሚመለከታቸው አካላት የተካተቱበትን የጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤቱን ያገለለ ነው ሲሉም ወቅሰዋል፡፡

ህውሃት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተግባር የፕሪቶርያውን ስምምነት የጣሰ ነው ማለቱ የሚታወስ ሲሆን በጠመንጃ ታግዞ መፈንቅለ ግዝያዊ አስተዳደር ያደረገው ህወሃት የፕሪቶሪያው ስምምነት ተጣሰ ማለቱ ውሃ የማያነሳ ጉዳይ ነው ሲሉ አቶ ጣዕመ ተችተዋል፡፡

ሌላው አስተያየታቸውን ለጣቢያችን የሰጡት የትግራይ ባይቶና ፓርቲ ሊቀመንበር ክብሮም በርሄ በበኩላቸው፣ ሁለቱም ወገኖች የፈጸሙት ድርጊት ህግን የተከተለ አይደለም ብለዋል፡፡

ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ያገለለ እና ያላማከረ መሆኑ አግባብነት የለውም ሲሉም አቶ በርሄ አክለው ተናግረዋል፡፡

ሀገሬ ቲቪ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...