‘’የፌደራል መንግስት ሊያማክረን ይገባል’’ የትግራይ ጊዜያዊ አማካሪ

Date:

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትን ህዝቡ እንዲመርጥ የሰጡት እድል ለዲሞክራሲ የቀረበ ቢሆንም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤቱን ያገለለ ነው ሲሉ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ለሃገሬ ቴሌቪዥን ቅሬታቸውን አቀረቡ፡፡

የትግራይ ነጻነት ፓርቲ የጽህፈት ቤት ሃላፊ ጣዕመ ሃጎስ፣ የፌደራል መንግስት የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትን ህዝቡ በኢሜይል እንዲመርጥ መጠየቃቸው ሌሎች ከክልሉ ውጪ ያሉ አካላትም እንዲመርጡ የሚያደርግ በመሆኑ ስህተት እንደሆነ አንስተዋል፡፡

አካሄዱ የተለያዩ የትግራይ ጉዳይ የሚመለከታቸው አካላት የተካተቱበትን የጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤቱን ያገለለ ነው ሲሉም ወቅሰዋል፡፡

ህውሃት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተግባር የፕሪቶርያውን ስምምነት የጣሰ ነው ማለቱ የሚታወስ ሲሆን በጠመንጃ ታግዞ መፈንቅለ ግዝያዊ አስተዳደር ያደረገው ህወሃት የፕሪቶሪያው ስምምነት ተጣሰ ማለቱ ውሃ የማያነሳ ጉዳይ ነው ሲሉ አቶ ጣዕመ ተችተዋል፡፡

ሌላው አስተያየታቸውን ለጣቢያችን የሰጡት የትግራይ ባይቶና ፓርቲ ሊቀመንበር ክብሮም በርሄ በበኩላቸው፣ ሁለቱም ወገኖች የፈጸሙት ድርጊት ህግን የተከተለ አይደለም ብለዋል፡፡

ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ያገለለ እና ያላማከረ መሆኑ አግባብነት የለውም ሲሉም አቶ በርሄ አክለው ተናግረዋል፡፡

ሀገሬ ቲቪ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...