የ2025 ግሎባል ሀንገር ኢንዴክስ ይፋ ሆነ

Date:

የሀገራትን የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ደረጃ የሚገመግመው የ’2025 ግሎባል ሀንገር ኢንዴክስ’ ጥናት በአፍሪካ ህብረት ዋና መሥሪያ ቤት በይፋ ተመርቋል።

በጥናቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ እንደተገለጸው፣ ዓለም ባለፉት ዓመታት በርሀብ ቅነሳና በምግብ ዋስትና ረገድ ተስፋ ሰጪ ስኬቶችን አስመዝግቦ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ከፍተኛ መሰናክሎች ተደቅነውበታል።

በተለይም በየአካባቢው የሚቀሰቀሱ ግጭቶች፣ እየተባባሰ የመጣው የአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም ተያያዥ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ቀውሶች የዘርፉን ጥረቶች እንዲጓተቱ ማድረጋቸው ተመላክቷል።

በመሆኑም ይህንን ፈታኝ ወቅት ለማለፍና የተጋረጡ ስጋቶችን ለመቀልበስ፣ በዘርፉ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በአዲስ ቁርጠኝነትና ስልታዊ በሆነ አመራር ሊደገፉ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

ወቅታዊው ሪፖርት ሀገራት የረሀብን አዙሪት ለመስበር ፖሊሲዎቻቸውን እንዲከልሱና ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ የሚያሳስብ ጠንካራ መልዕክት አስተላልፏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...