የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት ተጀመረ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ከዛሬ ሰኔ 8 እስከ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተለያዩ የፈተና ጣቢያዎች መሰጠት ጀምሯል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክብር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በዳግማዊ ሚኒሊክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት ፈተናውን በይፋ አስጀምረዋል።

👉🏼 85,017 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በከተማ ደረጃ ፈተናውን ይወስዳሉ።

👉🏼 በአጠቃላይ በ199 የፈተና ጣቢያዎች ፈተናው እየተሰጠ ይገኛል።

ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት ተዋቅሮ የጸጥታ አካላትና ልምድ ያላቸው አስፈጻሚዎች ተመድበዋል።

በከተማ አስተዳደሩ የተማሪዎች የምገባ አገልግሎት፣ የዩኒፎርምና የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉ ለውጤት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉ ተገልጿል። ዘንድሮም ከተደረገው ዝግጅት አንጻር የተሻለ ውጤት እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...

በጋምቤላ ክልል በጀት ዓመት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ2 ቢሊዮን በላይ ጭማሪ አሳየ

 በጋምቤላ ክልል በበጀት አመቱ በተከናወነው የገቢ አሰባሰብ ዙሪያ የተሻለ...