ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ሶማሊያ ገብተዋል

Date:

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ሞቃዲሾ አዳን አብዱል አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ አቀባበል እንዳደረጉላቸው የሶማሊያ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አደራዳሪነት ውጥረት ለማርገብ ከተስማሙ ወዲህ ሞቃዲሾ ሲገቡ የዛሬው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

በቆይታቸውም ከፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ ባለፈው አመት ሶማሊያ እንደ ግዛቷ አካል ከምትቆጥራት ሶማሊላንድ ጋር የተፈራረመችውን የመግባቢያ ሰነድ የአዲስ አበባ እና ሞቃዲሾን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማሻከሩ ይታወሳል።

ከአንድ አመት በላይ የዘለቀው ውጥረት በቱርክ አደራዳሪነት የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በአንካራ ፊትለፊት ከተገናኙ በኋላ መርገቡም አይዘነጋም።

በአንካራው ስምምነት መሰረትም የሁለቱ ሀገራት ባለስልጣናት ባለፉት ወራት በሞቃዲሾ እና በአዲስ አበባ በመገናኘት ንግግር ሲያደርጉ ቆይተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...

በኢትዮጵያ በካንሰር ከሚያዙ ሕፃናት መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ህክምና አያገኙም

በኢትዮጵያ በየዓመቱ በካንሰር ከሚጠቁ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ...