ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በስልክ ተወያይተዋል።
በውይይታቸው ማርኮ ሩቢዮ የኢትዮጵያ መንግስት ሰላሟ የተጠበቀና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየሰራ ላለው ስራ የአሜሪካ መንግስት ድጋፉን እንደሚያጠናክር ማረጋገጣቸውን ስቴት ዲፓርትመንት ድረገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
