“ህዳሴ ግድብ ከ1960ዎቹ የነፃነት ድል ወዲህ ለቀጠናው ሁለተኛው ድል ነው”

Date:

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከ1960ዎቹ ከቅኝ ግዛት ነፃ የመውጣት ድል ወዲህ ሁለተኛው ድል ነው ሲሉ የኢኮኖሚና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ተንታኝ ላውረንስ ፍሪማን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ በአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ትብብር ለማሳደግ ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው ያሉት ላውረንስ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በመገንባት አስደናቂ ስኬት ተቀዳጅታለች ብለዋል፡፡

ግድቡን ሁለት ጊዜ የመጎብኘት ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸው፤ ግድቡ የጋራ ትብብርን ከማሳደግ ውጪ ሌሎች ሀገራት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት አለመኖሩን አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያን በጋራ በመሆን ግድቡ እንዳይገደብ የሚደርስባቸውን ጫና መቋቋም ችለዋልም ነው ያሉት፡፡

አክለውም ”የግብጽ መሪዎች ከትብብር ይልቅ የዜሮ ድምር ፖለቲካ ያራምዳሉ” ያሉ ሲሆን፤ በዚህም ዓባይን በጋራ አልምቶ ከመጠቀም ይልቅ ኢትዮጵያን በጠላትነት ይፈርጃሉ ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የህዳሴ ግድብ በቀጠናው የሚያደርሰው ጉዳት ባይኖርም፤ ግብጾች ”ኢትዮጵያ ጠንካራ ከሆነች ሀገራችን ደካማ ትሆናለች” የሚል የተሳሳተ ግምት እንዳላቸው አብራርተዋል፡፡

ግብጽ ሁሌም በጂኦ-ፖለቲካ የበላይ የመሆን አመለካከት አላት፤ ይሄም በጋራ ለማደግ ከባድ እንቅፋት ከመሆን ያለፈ ጥቅም አልባ መሆኑን አንስተዋል።

ጋዜጣ ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ደቡብ ሱዳን የነዳጅ ቅድመ-ክፍያ ውሎችን እንዳትፈጽም አገደ

የለንደን ፍርድ ቤት ደቡብ ሱዳን ከአሁን በኋላ አዳዲስ የነዳጅ...

” ከ140 በላይ ጠጠር አምራች ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ ቆመዋል ” – ማህበሩ

" ካላቸው ቅሬታ ማቅረብ ይችላሉ። ግን መሬቱ መቼ እንደተወሰደባቸው...

ትራምፕ “በኢራን ላይ ሊፈጸም ታቅዶ የነበረውን ጥቃት አንፈጽምም” አሉ

ትራምፕ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ቁልፍ የአሜሪካ አጋር ሀገራት መሪዎች...

በነዳጅ ጭማሪ በኬንያ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ

በኬንያ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን ተከትሎ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ በጸጥታ...