ለኤሌክትሮኒክስ ደረሰኝ ሶፍትዌር አቅራቢዎች እስከ 250 ሺህ ዶላር ዋስትና

Date:

የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለመሰማራት በሚፈልጉ የኤሌክትሮኒክስ ደረሰኝ ሶፍትዌር አቅራቢዎች ላይ እንደ የደረጃቸው እስከ 250,000 የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የፋይናንስ ዋስትና የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ አውጥቷል።

በዚህ ወር አጋማሽ ላይ የወጣው መመሪያ በሀገሪቱ የታክስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ውስጥ የገበያ መግቢያ አዲስና ፈታኝ መስፈርት እንደሚሆን ይጠበቃል።

የዋስትናው መጠንም በአቅራቢው የአገልግሎት ዓይነትና በሚያገለግሉት ግብር ከፋዮች ልኬት ላይ ተመስርቶ በ10 ደረጃዎች የተከፋፈለ ነው።

በዚህም መሰረት የሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት አቅራቢዎች 30,000 ዶላር፣ የሶፍትዌር-አስ-አ-ሰርቪስ አቅራቢዎች 50,000 ዶላር፣ የኢ-ኮሜርስና ዲጂታል ገበያ አንቀሳቃሾች 25,000 ዶላር፣ እንዲሁም የራሳቸውን የውስጥ ደረሰኝ ሥርዓት የሚጠቀሙ ግብር ከፋዮች 15,000 ዶላር የባንክ ወይም የኢንሹራንስ ዋስትና ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።

የዋስትናው መጠንም አቅራቢዎች የሚያገለግሏቸው ደንበኞች ቁጥር ወይም የሽያጭ ልውውጣቸው እያደገ ሲሄድ በየሁለት ዓመቱ የሚታደስ ሲሆን፣ ከ40 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮችን ለሚያገለግሉ ወይም ከ1 ትሪሊዮን ብር በላይ ዓመታዊ ሽያጭ ላላቸው ድርጅቶች ከፍተኛው የዋስትና ጣሪያ 250,000 ዶላር ይደርሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...