ተጨዋቹ የማሊያ ቁጥሩን እንደሚለብስ ለማሳወቅ 18 አመት እስኪሞላው ድረስ የተጠበቀ ሲሆን መጪዎቹ ጊዜያት ለበረከት እና እርግማን ከመዘጋጀት በላይ እንደሆነ ተግልጿል ።
በቅርቡ 18 አመቱን ያከበረው ያማል ላለፉት 3 አመታት ሲለብሰው ከነበረው አንሱ ፋቲ ወደ ሞናኮ ማቅናቱን ተከትሎ የክለቡን ድንቅ ቁጥር ተረክቧል ።
ባሳለፍነው አመት ከባርሴሎና ጋር የላሊጋ ፣ የኮፓ ዴላሬይ እና የሱፐር ካፕ ዋንጫን ማሳካት የቻለው ተጨዋቹ በርካታ ጥቅም የሚስገኝለትን አዲስ ኮንትራትም ተፈራርሟል ።
ውሳኔው በክለቡ እና በተጨዋቹ መካከል በስምምነት የተደረገ ሲሆን በሚቀጥሉት ጊዜያትም የማሊያው ሽያጭ ላይ የገንዘብ ጭማሪ እንደሚኖረውም ተግልፅዋል።
