“ልሂቃኖቻችን” ያሏቸውን የኦሮሞ ፖለቲካ ተንታኞችን ነቀፉ

Date:


አቶ ሽመልስ ልሂቃኑ ላይ ነቀፋን ያቀረቡት የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) በሳምንቱ መጨረሻ በአዳማ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ነው።

በዚህን ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ “ልሂቃን ከሚባሉት አንዳንዶቹ የዶሮ ባህሪ ነው ያላቸው ብለዋል። ሽመልስ፤አንዳንዶቹ ልሂቃን ዶሮ የተሰጣትን እህል አስቀድማ እንደምትበትነው ሁሉ፤ የኦሮሞ ህዝብ ታግሎ አራት ኪሎ ያስገባውን በመበተን ኢንሶሎ፣ ሞያሌ እና ጊዳሚ ማስገባት ይፈልጋሉ” ሲሉ ተችተዋል።


ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በክልሉ አሁንም እልባት ስላላገኘው የፀጥታ ተግዳሮቶች ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ፤ የመንግስታቸው አቋም ከዚህ በፊት ከተቀመጠው አቋም ያልተለየ መሆኑን አስረድተዋል።

“የክልላችን መንግስት የህዝባችንን አንድነት ለመገንባት ያለውን የፖለቲካ ልዩነት በዘመናዊነት መንገድ እንዲመለስ ለማድረግ ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር ባደረገው ስምምነት ሰፊ ሃይል ገብቷል በየእለቱም እየገባ ነው፤ ለዚህ ትልቅ ክብር አለን፤ አሁንም በዚህ የተከበረ ጨፌ ፊት በቡድን ይሁን በተናጥል እንዲገቡ ዳግም ጥሪ ለማቅረብ እወዳለሁ ብለዋል።

ሽመልስ በመቀጠል የአንድም ሰው ህይወት እንዲጠፋ አንፈልግም፤ ከዚህ ቀደምም እንዳነሳነው ሁሉ የክልላችን መንግስትም ሆነ የፌዴራል መንግስት ከ100 ኪ.ሜ. 99 በመሄድ ለመቀበል ዝግጁ ነን” ብለዋል።

DW Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...