“ልሂቃኖቻችን” ያሏቸውን የኦሮሞ ፖለቲካ ተንታኞችን ነቀፉ

Date:


አቶ ሽመልስ ልሂቃኑ ላይ ነቀፋን ያቀረቡት የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) በሳምንቱ መጨረሻ በአዳማ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ነው።

በዚህን ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ “ልሂቃን ከሚባሉት አንዳንዶቹ የዶሮ ባህሪ ነው ያላቸው ብለዋል። ሽመልስ፤አንዳንዶቹ ልሂቃን ዶሮ የተሰጣትን እህል አስቀድማ እንደምትበትነው ሁሉ፤ የኦሮሞ ህዝብ ታግሎ አራት ኪሎ ያስገባውን በመበተን ኢንሶሎ፣ ሞያሌ እና ጊዳሚ ማስገባት ይፈልጋሉ” ሲሉ ተችተዋል።


ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በክልሉ አሁንም እልባት ስላላገኘው የፀጥታ ተግዳሮቶች ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ፤ የመንግስታቸው አቋም ከዚህ በፊት ከተቀመጠው አቋም ያልተለየ መሆኑን አስረድተዋል።

“የክልላችን መንግስት የህዝባችንን አንድነት ለመገንባት ያለውን የፖለቲካ ልዩነት በዘመናዊነት መንገድ እንዲመለስ ለማድረግ ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር ባደረገው ስምምነት ሰፊ ሃይል ገብቷል በየእለቱም እየገባ ነው፤ ለዚህ ትልቅ ክብር አለን፤ አሁንም በዚህ የተከበረ ጨፌ ፊት በቡድን ይሁን በተናጥል እንዲገቡ ዳግም ጥሪ ለማቅረብ እወዳለሁ ብለዋል።

ሽመልስ በመቀጠል የአንድም ሰው ህይወት እንዲጠፋ አንፈልግም፤ ከዚህ ቀደምም እንዳነሳነው ሁሉ የክልላችን መንግስትም ሆነ የፌዴራል መንግስት ከ100 ኪ.ሜ. 99 በመሄድ ለመቀበል ዝግጁ ነን” ብለዋል።

DW Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...

አሜሪካ እና እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ለአገሪቱ ጦር የማስረከብ ዕቅድ

አሜሪካ ድጋፏን በሰጠችው ዕቅድ መሠረት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የደቡብ...

የመሬት ልማትና አስተዳደር በበጀት ዓመቱ 63 በመቶ ያህሉን ማሳካት አልቻለም

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊገባደድ በተቃረበው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ...