አበዳሪው በቅርቡ ለኢትዮጵያ የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲሁም ለመንገድ እና ለኃይል ዘርፎች የ49.6 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ትናንት ከአዲሱ የባንኩ ፕሬዝዳንት አብዱላ አልሙሳአቤህ ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል፡፡
የባንኩ ኃላፊ ባንኩ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ልማትና ዕድገት በሚያፋጥኑና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች ድጋፉን ለማሳደግ ቁርጠኛ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ይህም ለአየር መንገዱ ግንባታ እንዲሁም ለኮይሻ ፕሮጅክት የገንዘብ ድጋፎች ማፈላለግን የተመለከተ እንደሆነ ማረጋገጣቸውንም የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
