ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከዱባዩ ዘ ፈርስት ግሩፕ ሆስፒታሊቲ ጋር ስትራቴጂካዊ ዉል ማሰሩ ተነገረ

Date:

የዱባዩ ግዙፍ የሆቴልና የእንግዳ ተቀባይነት አስተዳደር ድርጅት “ዘ ፈርስት ግሩፕ ሆስፒታሊቲ” ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር በተፈራረመው ታሪካዊ ስምምነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ በይፋ መግባቱን አስታውቋል።

በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ የወደፊት ሆስፒታሊቲ ጉባኤ ላይ የተፈረመው ይህ ስምምነት፤ በአዲስ አበባ፣ በሀዋሳ፣ በባህር ዳር፣ በጅማ፣ በላንጋኖ እና በደንቢ የሚገኙ 10 የሆቴልና የሪዞርት ፕሮጀክቶችን በጋራ ለማልማትና ለማስተዳደር ያለመ ነው።

ፕሮጀክቱ በራሱ ብራንድ የሚተዳደሩ እንዲሁም በዓለም አቀፉ የ”ማሪዮት” (Marriott) ሆቴል ስም የሚንቀሳቀሱ ሆቴሎችንና ሪዞርቶችን ያካተተ ሲሆን፤ ግንባታቸው ተጠናቆ ስራ ሲጀምሩም በአጠቃላይ 1,140 የሚሆኑ ዘመናዊ የመኝታ ክፍሎችን ለዘርፉ የሚያበረክቱ ሲሆን ከ2026 እስከ 2031 ባሉት ዓመታት ውስጥ በደረጃ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...