ማኅበሩ የአርበኞችን ታሪክ ሰንዶ ለማስቀመጥ የማሰባሰብ ሂደት ውስጥ ነዉ

Date:

አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞችም ቢሮ በመክፈት የአርበኞቹን ታሪክ በማደራጀት የተለያዩ ታሪካዊ ሰነዶችን የማሰባሰብ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ለአሐዱ ገልጿል።

የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፤ የአርበኞችን ቀን ከማክበር ባለፈ የአርበኞችን ታሪክ ሰንዶ ማስቀመጥ የታሪክ ክፍተትን ከመቀነስ አንጻር ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የአርበኞቹን ታሪክ ከማሰባሰብ በተጨማሪም፤ አሁን ላይ በሕይወት ያሉ አርበኞችን የመደገፍ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ታሪክ አሰባስቦ የመሰነዱን ሥራ ለማከናወን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል እየተደረገ ላለው ድጋፍ አመስግነው፤ የተደራጀ ሥራ ለመስራት የበጀት እጥረት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...