ፕሮጀክቱ የሚተገበረው በደብረብረሃን ከተማ ሲሆን 500 ለሚደርሱ ለችግሩ ተጋላጭ ህፃናት፣ ሴቶች ፣ አረጋውያን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ አስታውቋል።
በከተማዋ ከመንግሥት ተቋማት፣ ከማህበረሰቡ ፣ ከዳያስፖራ ኃብት በማሰባሰብ ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ፣ አረጋውያን እና ወጣቶች ተጠቃሚ የሚያደርግ የ15 ሚሊዮን ብር መፈረሙን የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መሥራች እና ዋና ሥራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ተናግረዋል።
ከደብረብርሀን ከተማ አስተዳደር ለዚሁ ሥራ የሚውል የመሬት ርክክብም የተደረገ ሲሆን የህፃናት ሁለገብ አገልግሎት የማዕከል ግንባታ ማስጀመሪያ የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ ሥነ ሥርዓትም ተካሂዷል።
በደብረ ብረሃን ተጋላጭ ህፃናትን ለመደገፍና የኩላሊት እጥበት አገልግሎት ለማስጀመር ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ እና ሄዋን ፋውንዴሽን የውል ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን ሔዋን ፋውንዴሽን ለኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚውል ቤት ለሜሪጆይ ማበርከቱን ሰምቷል፡፡
