ሞስኮና ቤጂንግ በሆርሙዝ ወሽመጥ ቀዉስ ሳቢያ ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸዉ ጠብቋል

Date:

በትራምፕ የውጭ ፖሊሲ እና በሆርሙዝ ወሽመጥ ቀውስ ሳቢያ ይበልጥ እየተቀራረበ የመጣው የሞስኮ እና የቤጂንግ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ጠብቋል ነዉ የተባለዉ፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቤጂንግን ጎብኝተው በወጡ በጥቂት ቀናት ውስጥ፣ ቻይና የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን በማስተናገድ ላይ ትገኛለች።

የትራምፕ የውጭ ፖሊሲ ሊገመት አለመቻል ሞስኮ እና ቤጂንግን ይበልጥ እያቀራረባቸው መሆኑን ተንታኞች ይገልጻሉ።

ይህ የሁለቱ አገራት ጥልቅ አጋርነት የመጣው በዩክሬን ጦርነት እና በኢራን ውጥረት ሳቢያ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በትራንስፖርት መስተጓጎል በተፈጠረው ቀውስ ነው።

ስትራቴጂካዊው የውሃ መስመር አደጋ ላይ በመውደቁ ቻይና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለማግኘት ይበልጥ ወደ ሩሲያ ፊቷን አዙራለች።

ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ ሁለቱንም መሪዎች በአንድ ሳምንት ልዩነት ማስተናገዳቸው በአጋጣሚ የተከሰተ እንዳልሆነ የሚናገሩት ተንታኞች፤ ይህም ቤጂንግ በተከፋፈለው የዓለም ሥርዓት ውስጥ ራሷን እንደ ታማኝና ተደማጭነት ያላት ተዋናይ አድርጋ ለማቅረብ የምታደርገውን ስትራቴጂካዊ ጥረት ያሳያል ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...