ሩሲያ ለኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድጋፍ ታደርጋለች

Date:

የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭ ከኢትዮጵያ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ጋር የበይነመረብ ውይይት ባደረጉበት ወቅት የሞስኮን ድጋፍ አረጋግጠዋል፡፡

“የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት በውይይቱ ተነስቷል። የሩሲያ ወገን የኢትዮጵያን እቅዶች ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍና የቴክኒክና የማማከር ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል” ሲል የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ከውይይቱ በኋላ ባወጣው መግለጫ ማስታወቁን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ሬሼትኒኮቭ የሩሲያና ኢትዮጵያ የንግድ ልውውጥ መጠን እያደገ መሄዱንም ጠቁመዋል። እ.ኤ.አ በ2025 የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ2.2 ጊዜ ጨምሮ 191.2 ሚሊየን ዶላር ደርሷል ብለዋል።

ሩሲያ በዋናነት ከኢትዮጵያ የቡና ምርት እያስገባች እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...