ሩስያ እና ሰሜን ኮሪያ የሚያገናኛቸው ድልድይ እየገነቡ ነው

Date:


ሩስያ እና ሰሜን ኮሪያ ተፈጥሯዊ ድንበራቸው በሆነው የቱመን ወንዝ ላይ ሁለቱን ሀገራት የሚያገናኛቸውን የመጀመሪያውን የድልድይ መንገድ መገንባት ጀምረዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቱ እየተጠናከረ የመጣው የሁለቱ ሀገራት አጋርነት መገለጫ ምልክት ነው ብለዋል ሀገራቱ።

የሩስያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሚኻይል ሚሹስቲን ፕሮጀክቱን ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሉት፥ መንገዱ የትራንስፖርት ወጪን ከመቀነስ በተጨማሪ በሁለቱ ሀገራት መካከል ንግድ እና ቱሪዝምን ያሳልጣል።

“ይህ በእርግጥም የሩስያ-ኮሪያ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ፕሮጀክት ነው”

ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሰሜን ኮሪያ ህዝባዊ ጠቅላይ ጉባኤ ሊቀመንበር ፓክ ታኤሶንግ ጋር በነበራቸው የቪዲዮ ውይይት።

ከምህንድስና ልህቀትነቱ ባሻገር ፋይዳው የጎላ ነው፤ በወዳጅነት ላይ የተመሰረተ መልካም ጉርብትናችንን ለማጠናከር እና ቀጣናዊ ትብብርን ለማጎልበት  ያለንን የጋራ መሻት ያንጸባርቃል ብለዋል።

በቱመን ወንዝ ላይ ግንባታው ከተጀመረው የድልድይ መንገድ በተጨማሪ እየዛገ ያለ የሶቪዬት ዘመን የባቡር ሐዲድ ድልድይ ይገኛል።

አዲሱ የድልድይ መንገድ ከአንድ ዓመት ተኩል በኋላ ሲጠናቀቅ ደግሞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ባነሰ የትራንስፖርት ወጪ የበለጠ የገቢ ወጪ ምርት ልውውጥ እንዲሁም የተሻለ የቱሪስት ፍሰት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ሚኻይል ሚሹስቲን።

ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...