ስለ ቦይንግ 737

Date:

የአሜሪካ ፍትሕ መስሪያ ቤት፣ ቦይንግ በኢትዮጵያና ኢንዶኔዥያ ከተከሰከሱት ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ጋር በተያያዘ “የማጭበርበር ወንጀል” ክሱን ላለመመስረት ከኩባንያው ጋር ከስምምነት መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል።

በስምምነቱ መሠረት፣ ቦይንግ በአውሮፕላኖቹ አመራረት ጥራት ላይ በውጭ ተቆጣጣሪ አካል የሚደረግበት ቁጥጥር እንደሚቀርለት ዘገባው ጠቅሷል። የተጎጂዎች ቤተሰቦች ጠበቆችና ሁለት የአሜሪካ ሴናተሮች፣ ክስ እንዳይቀር ጠይቀው ነበር።

ፍርድ ቤት፣ በሰኔ ወር ክሱን ለማየት ቀጠሮ ይዞ የነበረ ሲኾን፣ ቦይንግም “በማጭበርበር” ወንጀል ጥፈተኝነቱን እንደሚያምን ገልጦ ነበር። ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በላይ በቅጣትና ለተጎጂዎች በካሳ ይከፍላል። 

ዋዜማ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...