ስዊዘርላንድ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ አውሮፕላን

Date:

ስዊዘርላንድ በፀሐይ ኃይል ብቻ የሚሰራ አውሮፕላን ከ31,000 ጫማ በላይ ከፍታ በማብረር በአለም ታሪክ አዲስ ክብረወሰን ማስመዝገቧ ተገለጸ።

“ሶላርስትራቶስ” የተሰኘው ይህ ቀላል ክብደት ያለው አውሮፕላን፣ በንጹህ የፀሐይ ኃይል ብቻ የሚሰራ ሲሆን፣ ምንም አይነት ልቀት ሳያመነጭ እስከ 9,521 ሜትር (31,237 ጫማ) ከፍታ መድረስ ችሏል ነው የተባለው።

ይህ ታሪካዊ በረራ ዘላቂነት ያለው የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ምን ያህል እድገት እያሳየ እንደሆነ የሚያሳይ ትልቅ ምዕራፍ ነው ተብሎለታል።

የፕሮጀክቱ ዋና አብራሪ የሆኑት ራፋኤል ዶምጃን፣ አውሮፕላኑን ከስዊዘርላንድ ሲዮን አውሮፕላን ማረፊያ በማንሳት ይህንን የላቀ ብቃት ማሳየታቸው ተነግሯል።

አውሮፕላኑ በፀሐይ ኃይል እና በተፈጥሯዊ የአየር ሞገዶች ብቻ የሚበር መሆኑ፣ በአካባቢ ላይ ጉዳት የማያደርስ በረራ ምን ያህል ሊሳካ እንደሚችል ያሳያል ነው የተባለው።

ይህ ስኬት ንጹህ እና ለወደፊት ወደ ሰማይ ጠፈር ለመድረስ ለሚደረጉ የኤሮኖቲክስ ተልዕኮዎች አዲስ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።

የዓለም የአየር ስፖርት ፌዴሬሽን ይህንን መረጃ በይፋ ለማረጋገጥ ምርመራ እያደረገ ነው ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...