2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የወጣበትየኮሜዲ ድራማ ይዘት ያለው “ሹም ሽረት” ፊልም ከዛሬ ጀምሮ በተመረጡ ሲኒማ ቤቶች መታየት ይጀምራል።
የፊልሙ አዘጋጆች በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ ፊልሙ በዩሊያን ፊልም ፕሮዳክሽንናከክብሪት ፒክቸርስ ጋር በጥምረት የተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ፊልሙ በደራሲና ፕሮዲዩሰር ዩሊያን ተ/ማርያም ተደርሶ የቀረበ ሲሆን ዳይሬክትያደረገውም እራሱ ዩሊያን ተ/ማርያም ነው።
በፊልሙ ላይ አድማሱ ከበደ፣ ፍቅርተ ደሳለኝ፣ ማስተዋል ወንደሰን፣ ዩልያንተክለማርያም፣ ትዕግስት ከበደ፣ አብይ ዲንሳ እና ሌሎች ወጣት ተዋንያን ተሳትፈውበታል።
