በህንድ በደረሰ የድልድይ መደርመስ አደጋ 15 ሰዎች መሞታቸው ተሰማ፡፡
አደጋው የደረሰው በሀገሪቱ ጉጅራት በተባለ አካባቢ እንደሆነም ተገልጿል፡፡
የድልድዩ መደርመስ ምክንያት ባይጠቀስም፤ የሀገሪቱ ባለስልጣናት የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ሰዎችን ለመፈለግ የነፍስ አድን ሰራተኞች ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ሲነገር የድልድዩን መደርመስ ተከትሎ አራት ሰዎች የገቡበት እንዳልታወቀ ተገልጿል፡፡
የሀገሪቱ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ኮሚሽን በአደጋው የጠፉትን ሰዎች እና የሟቾችን አስከሬን እያፈላለግኩ ነው ማለቱን ቢቢሲ ዘግቧል።
