በጋብቻ ላይ ጋብቻ የመፈጸም ልማድን ማስቀረት አልተቻለም 

Date:

በጋብቻ ላይ ተጨማሪ ጋብቻን የመፈፀም ድርጊትን ለማስቀረት የተለያዩ ሥራዎች ቢሰራም ችግሩን አሁንም ድረስ መቅረፍ እንዳልተቻለ የጋምቤላ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታውቋል።

አንድ ወንድ ሦስትና አራት ሴቶችን የሚያገባበት ልማድ መኖሩን ያነሱት በቢሮው የሴቶችና ሕጻናት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ኦላንግ ጋች፤ ይህ ድርጊትም ሴቶች የሚቸገሩበት ጉዳይ ስለመሆኑ ገልጸዋል።

በክልሉ ይህንና ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ የሆኑ ድርጊቶችን ለማስቀረት የተጠናከረ ሥራ እንደሚሰራ አንስተው፤ ለውጥ እየታየባቸው ያሉ አንዳንድ ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡

ለአብነትም ያለ ዕድሜ ጋብቻ በብዛት የሚስተዋል እንደነበረ አስታውሰው፤ ለልጆች በየትምህርት ቤቱ ስልጠና በመስጠትና  የሐይማኖት አባቶችንም በማስተባበር ወላጆች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ በመሰራቱ ቀድሞ ከነበረበት እየቀነሰ ስለመምጣቱ አስታውቀዋል።

ነገር ግን አንድ ወንድ ከአንዲት ሴት በላይ የሚያገባበትን ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ለማስቀረት በተሰራው ሥራ የሚፈለገውን ያህል ለውጥ አለመምጣቱን ተናግረዋል፡፡

ማህበረሰቡን ከማስተማር ባለፈ በአመራር ደረጃ ያሉት ሰዎችን ድርጊቱን እንዳይፈፅሙ በመከልከል ለማስቀረት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...

ሕወሓት ድብረጺዮንን የክልሉ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

የክልሉ ፕሬዚዳንት ተደርገው የተመረጡት  ድብርጺዮን ገ/ ሚካዔል (ዶ/ር)  ቃለ...

” ኢራን ከምድረ ገጽ ትጠፋለች ” – ትራምፕ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ቴሌቪዥን ጋር ቃለ...

የአርበኞች ድል መታሰቢያ እና የዛሬው ትውልድ ለሕብረት ያለው አቋም

የጥንት ኢትዮጵያዊያንአርበኞች ድል 85 ኛው ዓመት መታሰቢያ ሚያዚያ...