በላይነህ ክንዴ ፊበላ ኢንዱስትሪያል የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ በኢትዮጵያ የትራንስፖርት አገልግሎት እድገትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፉ ላይ ጉልህ ሚና እየተወጣ ይገኛል። ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል ፈጥሯል።
በደብረ ብርሃን ከተማና ገላን ከተሞች በሚገኙ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መካከለኛና ከፍተኛ ተሽከርካሪዎችን በማምረት ለገበያ አቅርቧል። እያቀረበም ይገኛል።
ቢኬጂ የኢትዮጵያን ትራንስፖርት ችግር ማቃለል ባሻገር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ እሴት እየጨመረ ያለ ግሩፕ ነው።
በተለይም በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በማምረት የአካባቢ አየር ብክለትን ከመከላከል በተጨማሪ በከፍተኛ የውጭ ምንዛ የሚገባውን የነዳጅ ፍጆታ በማስቀረት አይነተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ከመለስተኛ እስከ ከፍተኛ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ የጭነት ተሽከርካሪዎችንና ቦቴዎችን አምርቶ ለሀገሩ ኢትዮጵያ አቅርቧል። እያቀረበና እያመረተም የሚገኝ ፋብሪካ ነው።
በላይነህ ክንዴ (BKG) የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት!
