በመዲናዋ ከ1መቶ 22 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በደንብ መተላለፍ ተቀጡ

Date:

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በባለፉት ዘጠኝ የበጀት ወራት 40 መንገዶች ላይ ቁጥጥር ማድረጉን ተናግሯል።

ተደርጓል በተባለዉ ቁጥጥር 1መቶ22 ሺህ 9 መቶ 57 አሽከርካሪዎች የደንብ መተላለፍ ቅጣት የተጣለባቸዉ መሆኑን ገልጿል።

ከፍጥነት ወሰን በላይ ሲያሽከርከሩ የተገኙ ከ80 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች፣ ከተፈቀደው የአልኮል መጠን በላይ ጠጥተው የተገኙ 1 ሺህ 6 መቶ 53 አሽከርካሪዎች ላይ የእርምት እርምጃ ወስጇለሁ ብሏል።

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት የደህንነት ቀበቶ ሳያደርጉ አገኘኋቸው ያላቸዉን 3ሺህ 66 ደንብ ተላላፊዎች፣በተመሳሳይ የጭንቅላት መከላከያ ቆብ ያላሰሩ 5 መቶ 85 የሞተር ብስክሌተኞችም እንደጥፋታቸው ደረጃ እንዲታረሙ መደረጉን ተናግሯል።

በተመሳሳይ 7 ሺህ 26 አሽከርካሪዎች ስልክ እያነጋገሩ አደባባዮች ላይ እና በመስቀለኛ መንገዶች ላይ ምጽዋት የሰጡ እና ግብይት የፈጸሙ 4 ሺህ 5መቶ ግለሰቦችም በዚህ ደንብ መተላላፍ መቀጣታቸዉ ተገልጿል።

ተቋሙ በዚህ ቁጥጥር ከ37 ሺህ በላይ እግረኞችም በደንብ መተላለፍ ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረጉን አሳዉቋል።

መንገድ አጠቃቀም ዙሪያ በተደረገ ቁጥጥር ማድረጉን በመግለጽ 21ሺህ 2መቶ2 እግረኞች በገንዘብ መቀጣታቸዉን ተቋሙ ገልጿል።

16 ሺህ 6 መቶ 51 እግረኞች የተላለፉትን የመንገድ አጠቃቀም ደንብ በማህበራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ስለመቻሉ አያይዞ ገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት 7 መቶ 43 መኪኖች በክሬን ተነስተዉ ለትራፊክ ፍሰቱ ምቹ እንዲሆን ስለማድረጉ አሳዉቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...