በመዲናዋ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ባለው የመንገድ ሃብት ላይ ጉዳት ደርሷል

Date:

የአዲስአበባ መንገዶች ባለስልጣን በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በተሽከርካሪዎች ግጭት ሳቢያ ከ 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን አስታወቀ

ባለስልጣኑ ከጉዳት አድራሾችና ከሌሎች የመንገድ ጉዳት ካሣ ክፍያዎች ከ23 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ ሰብስቧል ተብሏል።

ባለፉት 9 ወራት በአጠቃላይ 182 የግጭት አደጋዎች የደረሱ መሆኑን ተቋሙ ገልፆል።

51 የሚሆኑት በቀለበት መንገድ ላይ የተከሰቱ ሲሆን፣ 131 የግጭት አደጋዎች ደግሞ ከቀለበት መንገድ ውጪ ባለው የከተማዋ መንገዶች ላይ የደረሰ ጉዳት መሆኑን አስታዉቋል።

በእግረኛ መንገዶች ላይ የግንባታ ግብዓትና ተረፈ ምርት ባከማቹና ሌሎች የመንገድ መብት ጥሰቶች በፈፀሙ አካላት እርምጃ ወስጃለሁ ብሏል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በተሽከርካሪ ግጭት ምክንያት ጉዳት የደረሰበትን የመንገድ ሀብት በመጠገን ላይ እንደሚገኝ በስራ አፈፃፀሙ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...