በሱዳን ካርቱም ግዛት የተቀሰቀሰው የኮሌራ ወረርሺኝ በአካባቢው በተፈጥረ የውሃ መበከል እንዲሁም የውሃ አጥረት መባባሱ ተገለፀ፡፡
በሱዳን መዲና ካርቱም በተፈጠረው የውሃ እጥረት ሳቢያ ማህብረስቡ በቀጥታ የአባይን ውሃ ለመጠጥነት ለመጠቀም እየተገደደ እንደሆነ ሱዳን ቱሪቡን አስነብቧል፡፡
በከተማው ውስጥ በተቋቋመው የአስቸኳይ ግዜ መልስ መስጫ ሆሰፒታል ወሰጥ ሃሙስ እለት ብቻ ከ200 በላይ አዳዲስ ታካሚዎች እንደገቡ ሆስፒታሉ በፌስ ቡክ ገጹ አስታውቋል፡፡
ውረርሽኙ አሁን ላይ በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች እየተስፋፋ በደቡብ ኦምዱርማን በነጭ አባይ አካባቢ በስፋት እየተሰራጨ እንደሚገኝ የተባብሩት መንግስታት ድርጅት ገልጿል፡፡
በቀጣይ የፊደራል መንግስት እና አለም አቅፍ ተቋማት ደጋፍ ካላድረጉ ችግሩ መባባሱ እንደማይቀር ሆስፒታሉ አስታውቋል፡፡
