በበጀት ዓመቱ ከ50 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር ተቀጥተዋል

Date:

በጀት ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ ከ50 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር መቀጣታቸውን የመዲናዋ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ዳይሬክተር አቶ ከበበው ሚዴቅሳ እንደገለጹት፤ ሕግ የሚጥሱ አሽከርካሪዎች ላይ የቁጥጥር ሥራዎች ተሠረርተዋል።

በዚህም ከ50 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ አሽከርክረው ተቀጥተዋል ብለዋል።

በተጨማሪም 7 ሺህ 643 ደህንነት ቀበቶ ያላደረጉ አሽከርካሪዎች፣ 746 ሞተር አሽከርካሪዎች ያለሄልመት በማሽከርከር፣ 41 ሺህ 373 የብዙሀን ትራንስፖርት መጫኛና ማውረጃ ላይ ተሽከርካሪ በማቆም እንዲሁም የሚከለክሉ ቦታዎች ላይ የቆሙ 33 ሺህ 638 አሽከርካዎች የተቀጡ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በአጠቃላይ በተሰራ የትራፊክ የሕግ ማስከበር እና የቁጥጥር ስራ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ደንብ በመተላለፍ ተቀጥተዋል ሲሉ አብራርተዋል፡፡

ከአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ጋር በመሆን 19 ሺህ 192 ተሽከርካሪዎች ላይ ድንገተኛ የመንገድ ላይ የቴክኒክ ምርምራ የተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ከነዚህም ውስጥ የቴክኒክ ጉድለት ያለባቸው 3 ሺህ 220 አሽከርካሪዎች እንዲቀጡ ተደርል ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...