በትግራይ ክልል በኮሌራ በሽታ የአምስት ሰዎች ህይወት አለፈ

Date:

በትግራይ ክልል ሰለዋ፣ ሳምረ እና ሰየምቲ አድያቦ በተሰኙ ሶስት ወረዳዎች ላይ ባጋጠመ የኮሌራ ወረርሽኝ 161 ሰዎች የተጠቁ ሲሆን 46 ሰዎች በፅኑ መታመማቸውን የክልሉ የጤና ቢሮ አስታውቋል።

ብስራት ከትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ያገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነም ከአጠቃላይ ተጠቂዎቹ ሰባቱ የህክምና ክትትል እየተደረጋላቸው ሲሆን 149 ሰዎች በተደረገላቸው ህክምና አገግመው ወደ ቤታቸው ተሸኝተዋል።

ወረርሽኙ ባጋጠመባቸው ሶስቱ ወረዳዎች እስከ ነሀሴ 17 ቀን 2017 ዓ/ም ባለው ጊዜ ውስጥ በአጠቃላይ የአምስት ሰዎች ሞት መመዝገቡም የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል።

ከሟቾቹ መካከል ሁለቱ የሳምረ ነዋሪ የሆኑ አባት እና ልጅ ሲሆኑ ከአባትየው በተወሰደ ናሙና የተደረገ ምርመራ ኔጋቲቭ ሆኖ መገኘቱ ተገልፆል።

የግልና የአከባቢ ፅዳት አለመጠበቅ ዋንኛ የበሽታው መንስኤ ነው ያለው ቢሮው ማህበረሰቡ ግላዊና የአከባቢ ፅዳት መጠበቅ፣ የሚጠጣ ውሃ ብሎም ምግብ ፅዳት መጠበቅ፣ ሁልጊዜ መፀዳጃ ቤት መጠቀምና በአግባቡ ማፅዳት፣ እንዲሁም በወሳኝ ሰዓታት እጆችን በዉሃና በሳሙና በሚገባ መታጠብ ወረርሽኙን ለመግታት ቁልፍ መሆናቸው ብስራት ከትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ያገኘው መረጃ አሳይቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...